Telegram Group & Telegram Channel
😘ሰሜናዊት ሙሽራ😘

🔥ክፍል 19

✍ደራሲ ዮሴፍ ተሾመ
.
.
.
ሁለተኛው ሴሚስተር ተጠናቆ እነ ዮርዳኖስ ወደ እየቤተሰቦቻቸው ለመሔድ ዛሬ የመጨረሻ ቀን ነች።እነ ዮርዳኖስ ዶርም አዲስ ተዓምር ተፈጥሯል።ዞላ በጩቤ ከተወጋ በኋላ አዲስ ሰው ሆኖአል ሱስ ለምኔ ብሎ አብረውት የነበሩትን ደባል ሱሶች አራግፎ አዲስ ህይወት አዲስ ምዕራፍ አዲስ እርምጃ በሚል መርህ ሙሉ ጊዜውን ለትምህርቱ እና ለጓደኞቹ ሰጥቷል።ሙሉ የዶርሙ ተማሪ ደስታ ተሞቷል ።የዮኒ ጎጄንም ምስጢር ተዘርግፏል።ቀን ያደረገውን ሁሉ ሌሊት ሲቃዥ የሚያድረው ዜኖ በእንቅልፍ ልቡ ሲቃዥ ናቲ ሰምቶ እርፍ።
እንዲህ ሆነ።
የእነ ዜኖ ክላስ ልጅ ገሊላ እምትባል ውብ የሆነች ልጅ አለች።ዮኒ ጎጄ ፍቅር የለም ሲል የነበረው ልጅ ወደዳት እና እርፍ።ከዚያም ዜኖ እና ገሊላ አንድ ክላስ ስለሆኑ ዜኖ የገሊላ ስልክ አለው።ዮኒ ጎጂ ቀለል አድርጎ ዜኖ የገሊላን ስልክ ስጠኝ ይለዋል።ዜኖም አንተ ምን አባህ ሊያደርግልህ።አለ ዜኖ። ዮኒ ጎጄም አንድ ጉዳይ ነበረኝ ስጠኝ ሲል።ዜኖ ምክንያት ካልነገርከኝ ብሎ ድርቅ ማለቱን ተከትሎ ዮኒ ጎጄም ምስጢር ነው እሺ እንዳትናገር የእነ ዮርዲን ፉገራ አልችለውም።ሳልወዳት አልቀርም ።አለ ዮኒ ጎጄ ።ዜኖም ስልክ ቁጥሯን ሰጠው ።
በማግስቱ ሁሉም የዶርሙ ተማሪዎች ቀን ላይ ተኝተው ናቲ አሳይመንት እየሰራ ነበር።ከዛም ዜኖ መቃዠት ጀመረ።
"እ.እ እእእእ ዮኒ ጎጄ ገሊላን ...እእእእ....ከልብህ....አፍቅረሀት .....አአአአአአ....ነው "እያለ የቃዠውን ናቲ ሰማ።
ማታ ሁሉም በተሰባሰቡበት ናቲ "አንተ ዮርዲ ገሊላን ታውቃታለህ እንዴ?" አለ።ሆን ብሎ ነበር እንደዛ ያለው።
ዮኒ ጎጄ ዜኖ ጋር አፈጠጠበት።ዜኖም "ማርያም ዮኒ ጎጄ አልተናገርኩም" አለ።
"ምንድንነው የምታወሩት" አለ ዮርዲ ግራ ተጋብቶ።
ናቲ ሁሉንም ነገር ዝርግፍ አድርጎ ተናገረ።በዮኒ ጎጄ የተወሰነ ቀን ከሳቁበት በኋላ ሁለቱን አንድ የማድረግ እቅድ ነድፈው መንቀሳቀስ ጀመሩ።ገሊላ ቀድማ በዮኒ ጎጄ ታማሚ ሆና አገኟት። እቅዳቸው ሰመረ።ፍቅር የለም እያለ ቱሪናፋውን ሲነፋ የነበረ ልጅ በፍቅር አለም ሰጠመ።በፍቅር አክናፍ በረረ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
"ዮርዲዬ በቃ ነገ እኮ አገር ቤት ልትገባ ነው።ናፍቆትህንም ልታገኛት ነው"አለ ዮኒ
"ምን ባክህ ሔዋን ምን እንደነካት አላውቅም ስልክ አትደውልም ስደውልላትም ደስተኛ አይደለችም ደስ ሲላትም ስልክ አታነሳም"አለ ዮርዲ እዝን ብሎ
"ምነው አለች?"አለ ዮኒ
"እኔ እንጃ ልቤ ፈርቷል።ውስጤ ተረብሿል የሆነ ነገር እንደሚፈጠር እየነገረኝ ነው።ለመልካም ይሁን እንጂ "አለ ዮርዲ
"ፈጣሪ የፈቀደው ነው እሚሆነው።ለማንኛውም ልቦለድህን እንዴት እንደወደድኩት አትጠይቀኝ"አለ ዮኒ
"አረ እውነትህን ነው"አለ ዮርዲ
"እውነት ለማንኛውም ኮሜንት ፅፌ ውስጥ አስቀምጬልሀለው "አለ ዮኒ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እነ ዮርዳኖስ ዮኒቨርስቲ ላይ አንድ አመት በፍቅር በመተሳሰብ አስቆጥረው ወደ እየቤተሰቦቻቸው ተበታተኑ።ዮኒቨርሲቲ ህይወትን ተምረውበታል።ልዩነትን ውበት አድርገው በአንድነት ከሌሎች ብሔሮች ጋር ዘምረው።ባህል ወግ ቋንቋን አካፍለው ከሌሎች ደግሞ ቀስመው።ማህበራዊነትን መቻቻልን ከትምህርታቸው በበለጠ ተምረው ሔዱ።


ዮርዳኖስ ሲጓዝ ውሎ አመሻሽ አስራ ሁለት ሰዐት አካባቢ ነበር የገባው።በጉዞው በመድከሙ የተነሳ ቤተሰቦቹን እንኳን በቅጡ አላጫወታቸውም።ሻወር ወስዶ እራት እንደነገሩ ከቀማመሰ በኋላ ክፍሉ ገብቶ ተኛ።ሰላም ያለው እንቅልፍ ወሰደው።የንጋት ጎህ ተቀዶ የወፎች ዝማሬ እና የጊወርጊስ ቤተክርስቲያን ጥዑም የቅዳሴ ዜማ በአንድነት ተደምሮ ዮርዳኖስን ቀሰቀሰው።አልተናደደም ።ምክነያቱም እልፍ አዕላፍ ህዝብ በሁካታ በግርግር በኑሮ የትግል ሽኩቻ ውስጥ ሲዋከብ ውሎ የደከመ ጎኑን ለማሳረፍ ወደቤቱ ሲገባ የክለብ ዳንኪራ ጩኸት፣የግሮሰሪዎች ክፍት አፍነት፣የመሸታ ቤቶቹ ከአቅም በላይ ጫጫታ፣የባህል ምሽቶች አፈኛ አዝማሪ አላስተኛ ብለውት ሲገላበጥ አምሽቶ ሲነጋጋ ደግሞ በቁርስ ቤቶች ሙዚቃ የሚቀሰቀሰውን ምስኪን ህዝብ ማሰብ በቂ ነው። ዮርዲ ግን ለብዙ ወራት ሲናፍቀው የከረመው የጊወርጊስ ጥዑመ ዜማ ነው ያባነነው።እድለኛ ነው።
ፊቱን ታጠበና ቅዱስ ጊወርጊስን ተሳልሞ ሊመለስ ወደ ጊወርጊስ ሔደ።ከቤተሰቦቹ ጋር በሰላም ያገናኘውን ቅዱስ ጊወርጊስን አመስግኖ ከተመለሰ በኋላ ቁርስ ከቤተሰቦቹ ጋር ተመግቦ ወደ እነ ሔዋን ቤት አመራ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፧፧፧፧፧፨፨፨፨፨፨፨፨
ዮርዲ ለሔዋን እና አባት ሰላምታውን አቅርቦ አብርሀምን ከልብ በመነጨ ፍፁም ወንድማዊነት በተሞላበት አስተቃቀፍ አቀፈውና ሰላምታ ሰጥቶት ተቀመጠ።
ሔዋን ፍለጋ አይኑን ቢያማትርም ሔዋንን ሊያያት አልቻለም።
"ምነው መምጣትህን እኮ ሔዋን አልነገረችንም"አለ አቶ አንድነት
"አዎ ስደውልላት ስልክ አታነሳም ነበር"አለ ዮርዲ
"ስራው አጨናንቋት ይሆናል"ብሎ አቶ አንድነት ወንድሟ ምናሴ ከአሜሪካ ተመልሶ አዲሱ የእርዳታ ድርጅት ውስጥ ተቀጥረው መስራት እንደጀመሩ ነገረው።
፨፧፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ዮርዳኖስ ከእነ ሔዋን ቤት ከተመለሰ በኋላ ለሔዋን ደወለላት እና መምጣቱን ነገራት።ምሳ ሰዐት ላይ ስትመለስ እንደምትደውልለት ነግራው ስልኩን ዘጋችው።ሔዋን መምጣቴን ስትሰማ በደስታ እየጨፈረች ትመጣልኛለች ብሎ የጠበቀው ዮርዲ በተቃራኒው ሲሆን የሆነ ዝብርቅርቅ ያለ ስሜት ውስጡን ወረረው።
ቃለአብ ላይ ደወለለት እና መምጣቱን ሲነግረው።የት ልምጣ ዮርዲዬ አለ ለማግኘት እየቸኮለ። ቴሌው ጋር እጠብቅሀለሁ አለ ዮርዲ።ይሔው ተነሳሁ አለና ቃል ስልኩን ዘጋው።
ዮርዲ ሔዶ ቴሌው ፊት ለፊት ካለው የቲቪ ፓርክ መቀመጫ ላይ ተቀመጠና ቃልን በጉጉት መጠበቅ ጀመረ።ባለብስክሌቱ ቃለአብ ብስክሌቱን እያበረረ መጥቶ ዮርዲ አቀርቅሮ በተቀመጠበት ቦታ ላይ ዱብ አለ።ዮርዲ ቃል ከሰማይ የተከሰተ መሰለው።ሲያየው በፊት ይረበሽ እንደነበረው አሁንም ያ ስሜቱ አልተወውም ልቡ መታች።ቃል እቅፍ አደረገው ዮርዲም አቀፈው።ለደቂቃዎች ያህል ተቃቅፈው ከቆዩ በኋላ ቃል ዮርዲን ቀና አደረገውና ግንባሩ ላይ ሳም አደረገው። ተቀምጠው አወሩ አወጉ።ናፍቆታቸውን አይን አይን እየታያዩ ተወጡ።ቃለአብ ትምሀርት አቁሞ የእርዳታ ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ እየሰራ እንደሆነ ነገረው።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
"ዮርዲዬ ዛሬ ማዘሪቱን አስተዋውቅሀለሁ ተነስ እንሒድ"አለ
"አንተ ያምሀል እንዴ እኔ ትልቅ ሰው በጣም ነዉ እምፈራው።ደግሞ ምንድነው ብለህ ነው እምታስተዋውቀኝ"አለ ዮርዲ
"ዮርዲ ወንድሜ እኮ ነህ ።ምን ብየ እንዳስተዋውቅህ ነበር የፈለግከው?አሁን በል ተነስ"ብሎ ቃለ አብ ድርቅ አለ።
ዮርዲ እና ቃለአብ ግራና ቀኝ ሁነው ብስክሌቷን እየገፉ ወደ እነ ቃል ቤት አመሩ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ማርዘነብ ግሮሰሪ እንደደረሱ "ይቺ ናት ግሮሰሪያችን መተዳዳሪያችን።"አለ ቃል።
ከግሮሰሪው ጎን ባለው የግቢያቸው በር ወደ ዋናው ቤታቸው ዮርዲን ይዞት ገባ እና ቤት አስቀምጦት ወደ ግሮሰሪው ማርዘነብን ለመጥራት ገባ።
"እማዬ ዛሬ ወንድሜ ነው እያልኩሽ የነበረውን ጓደኛዬን አስተዋውቅሻለሁ።"ብሎ ወደቤት ማርዘነብን እየጎተተ ይዟት ገባ።
ማርዘነብ ዮርዲን እንዳየችው በድንጋጤ ክው ብላ ቀረች።መደንገጧ እንዳይታወቅባት "እእ......እ..አንተ ነህ የቃል ጓደኛ?"አለች የግዷን ፈገግ ብላ።



tg-me.com/yegna_mastawesha/29
Create:
Last Update:

😘ሰሜናዊት ሙሽራ😘

🔥ክፍል 19

✍ደራሲ ዮሴፍ ተሾመ
.
.
.
ሁለተኛው ሴሚስተር ተጠናቆ እነ ዮርዳኖስ ወደ እየቤተሰቦቻቸው ለመሔድ ዛሬ የመጨረሻ ቀን ነች።እነ ዮርዳኖስ ዶርም አዲስ ተዓምር ተፈጥሯል።ዞላ በጩቤ ከተወጋ በኋላ አዲስ ሰው ሆኖአል ሱስ ለምኔ ብሎ አብረውት የነበሩትን ደባል ሱሶች አራግፎ አዲስ ህይወት አዲስ ምዕራፍ አዲስ እርምጃ በሚል መርህ ሙሉ ጊዜውን ለትምህርቱ እና ለጓደኞቹ ሰጥቷል።ሙሉ የዶርሙ ተማሪ ደስታ ተሞቷል ።የዮኒ ጎጄንም ምስጢር ተዘርግፏል።ቀን ያደረገውን ሁሉ ሌሊት ሲቃዥ የሚያድረው ዜኖ በእንቅልፍ ልቡ ሲቃዥ ናቲ ሰምቶ እርፍ።
እንዲህ ሆነ።
የእነ ዜኖ ክላስ ልጅ ገሊላ እምትባል ውብ የሆነች ልጅ አለች።ዮኒ ጎጄ ፍቅር የለም ሲል የነበረው ልጅ ወደዳት እና እርፍ።ከዚያም ዜኖ እና ገሊላ አንድ ክላስ ስለሆኑ ዜኖ የገሊላ ስልክ አለው።ዮኒ ጎጂ ቀለል አድርጎ ዜኖ የገሊላን ስልክ ስጠኝ ይለዋል።ዜኖም አንተ ምን አባህ ሊያደርግልህ።አለ ዜኖ። ዮኒ ጎጄም አንድ ጉዳይ ነበረኝ ስጠኝ ሲል።ዜኖ ምክንያት ካልነገርከኝ ብሎ ድርቅ ማለቱን ተከትሎ ዮኒ ጎጄም ምስጢር ነው እሺ እንዳትናገር የእነ ዮርዲን ፉገራ አልችለውም።ሳልወዳት አልቀርም ።አለ ዮኒ ጎጄ ።ዜኖም ስልክ ቁጥሯን ሰጠው ።
በማግስቱ ሁሉም የዶርሙ ተማሪዎች ቀን ላይ ተኝተው ናቲ አሳይመንት እየሰራ ነበር።ከዛም ዜኖ መቃዠት ጀመረ።
"እ.እ እእእእ ዮኒ ጎጄ ገሊላን ...እእእእ....ከልብህ....አፍቅረሀት .....አአአአአአ....ነው "እያለ የቃዠውን ናቲ ሰማ።
ማታ ሁሉም በተሰባሰቡበት ናቲ "አንተ ዮርዲ ገሊላን ታውቃታለህ እንዴ?" አለ።ሆን ብሎ ነበር እንደዛ ያለው።
ዮኒ ጎጄ ዜኖ ጋር አፈጠጠበት።ዜኖም "ማርያም ዮኒ ጎጄ አልተናገርኩም" አለ።
"ምንድንነው የምታወሩት" አለ ዮርዲ ግራ ተጋብቶ።
ናቲ ሁሉንም ነገር ዝርግፍ አድርጎ ተናገረ።በዮኒ ጎጄ የተወሰነ ቀን ከሳቁበት በኋላ ሁለቱን አንድ የማድረግ እቅድ ነድፈው መንቀሳቀስ ጀመሩ።ገሊላ ቀድማ በዮኒ ጎጄ ታማሚ ሆና አገኟት። እቅዳቸው ሰመረ።ፍቅር የለም እያለ ቱሪናፋውን ሲነፋ የነበረ ልጅ በፍቅር አለም ሰጠመ።በፍቅር አክናፍ በረረ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
"ዮርዲዬ በቃ ነገ እኮ አገር ቤት ልትገባ ነው።ናፍቆትህንም ልታገኛት ነው"አለ ዮኒ
"ምን ባክህ ሔዋን ምን እንደነካት አላውቅም ስልክ አትደውልም ስደውልላትም ደስተኛ አይደለችም ደስ ሲላትም ስልክ አታነሳም"አለ ዮርዲ እዝን ብሎ
"ምነው አለች?"አለ ዮኒ
"እኔ እንጃ ልቤ ፈርቷል።ውስጤ ተረብሿል የሆነ ነገር እንደሚፈጠር እየነገረኝ ነው።ለመልካም ይሁን እንጂ "አለ ዮርዲ
"ፈጣሪ የፈቀደው ነው እሚሆነው።ለማንኛውም ልቦለድህን እንዴት እንደወደድኩት አትጠይቀኝ"አለ ዮኒ
"አረ እውነትህን ነው"አለ ዮርዲ
"እውነት ለማንኛውም ኮሜንት ፅፌ ውስጥ አስቀምጬልሀለው "አለ ዮኒ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እነ ዮርዳኖስ ዮኒቨርስቲ ላይ አንድ አመት በፍቅር በመተሳሰብ አስቆጥረው ወደ እየቤተሰቦቻቸው ተበታተኑ።ዮኒቨርሲቲ ህይወትን ተምረውበታል።ልዩነትን ውበት አድርገው በአንድነት ከሌሎች ብሔሮች ጋር ዘምረው።ባህል ወግ ቋንቋን አካፍለው ከሌሎች ደግሞ ቀስመው።ማህበራዊነትን መቻቻልን ከትምህርታቸው በበለጠ ተምረው ሔዱ።


ዮርዳኖስ ሲጓዝ ውሎ አመሻሽ አስራ ሁለት ሰዐት አካባቢ ነበር የገባው።በጉዞው በመድከሙ የተነሳ ቤተሰቦቹን እንኳን በቅጡ አላጫወታቸውም።ሻወር ወስዶ እራት እንደነገሩ ከቀማመሰ በኋላ ክፍሉ ገብቶ ተኛ።ሰላም ያለው እንቅልፍ ወሰደው።የንጋት ጎህ ተቀዶ የወፎች ዝማሬ እና የጊወርጊስ ቤተክርስቲያን ጥዑም የቅዳሴ ዜማ በአንድነት ተደምሮ ዮርዳኖስን ቀሰቀሰው።አልተናደደም ።ምክነያቱም እልፍ አዕላፍ ህዝብ በሁካታ በግርግር በኑሮ የትግል ሽኩቻ ውስጥ ሲዋከብ ውሎ የደከመ ጎኑን ለማሳረፍ ወደቤቱ ሲገባ የክለብ ዳንኪራ ጩኸት፣የግሮሰሪዎች ክፍት አፍነት፣የመሸታ ቤቶቹ ከአቅም በላይ ጫጫታ፣የባህል ምሽቶች አፈኛ አዝማሪ አላስተኛ ብለውት ሲገላበጥ አምሽቶ ሲነጋጋ ደግሞ በቁርስ ቤቶች ሙዚቃ የሚቀሰቀሰውን ምስኪን ህዝብ ማሰብ በቂ ነው። ዮርዲ ግን ለብዙ ወራት ሲናፍቀው የከረመው የጊወርጊስ ጥዑመ ዜማ ነው ያባነነው።እድለኛ ነው።
ፊቱን ታጠበና ቅዱስ ጊወርጊስን ተሳልሞ ሊመለስ ወደ ጊወርጊስ ሔደ።ከቤተሰቦቹ ጋር በሰላም ያገናኘውን ቅዱስ ጊወርጊስን አመስግኖ ከተመለሰ በኋላ ቁርስ ከቤተሰቦቹ ጋር ተመግቦ ወደ እነ ሔዋን ቤት አመራ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፧፧፧፧፧፨፨፨፨፨፨፨፨
ዮርዲ ለሔዋን እና አባት ሰላምታውን አቅርቦ አብርሀምን ከልብ በመነጨ ፍፁም ወንድማዊነት በተሞላበት አስተቃቀፍ አቀፈውና ሰላምታ ሰጥቶት ተቀመጠ።
ሔዋን ፍለጋ አይኑን ቢያማትርም ሔዋንን ሊያያት አልቻለም።
"ምነው መምጣትህን እኮ ሔዋን አልነገረችንም"አለ አቶ አንድነት
"አዎ ስደውልላት ስልክ አታነሳም ነበር"አለ ዮርዲ
"ስራው አጨናንቋት ይሆናል"ብሎ አቶ አንድነት ወንድሟ ምናሴ ከአሜሪካ ተመልሶ አዲሱ የእርዳታ ድርጅት ውስጥ ተቀጥረው መስራት እንደጀመሩ ነገረው።
፨፧፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ዮርዳኖስ ከእነ ሔዋን ቤት ከተመለሰ በኋላ ለሔዋን ደወለላት እና መምጣቱን ነገራት።ምሳ ሰዐት ላይ ስትመለስ እንደምትደውልለት ነግራው ስልኩን ዘጋችው።ሔዋን መምጣቴን ስትሰማ በደስታ እየጨፈረች ትመጣልኛለች ብሎ የጠበቀው ዮርዲ በተቃራኒው ሲሆን የሆነ ዝብርቅርቅ ያለ ስሜት ውስጡን ወረረው።
ቃለአብ ላይ ደወለለት እና መምጣቱን ሲነግረው።የት ልምጣ ዮርዲዬ አለ ለማግኘት እየቸኮለ። ቴሌው ጋር እጠብቅሀለሁ አለ ዮርዲ።ይሔው ተነሳሁ አለና ቃል ስልኩን ዘጋው።
ዮርዲ ሔዶ ቴሌው ፊት ለፊት ካለው የቲቪ ፓርክ መቀመጫ ላይ ተቀመጠና ቃልን በጉጉት መጠበቅ ጀመረ።ባለብስክሌቱ ቃለአብ ብስክሌቱን እያበረረ መጥቶ ዮርዲ አቀርቅሮ በተቀመጠበት ቦታ ላይ ዱብ አለ።ዮርዲ ቃል ከሰማይ የተከሰተ መሰለው።ሲያየው በፊት ይረበሽ እንደነበረው አሁንም ያ ስሜቱ አልተወውም ልቡ መታች።ቃል እቅፍ አደረገው ዮርዲም አቀፈው።ለደቂቃዎች ያህል ተቃቅፈው ከቆዩ በኋላ ቃል ዮርዲን ቀና አደረገውና ግንባሩ ላይ ሳም አደረገው። ተቀምጠው አወሩ አወጉ።ናፍቆታቸውን አይን አይን እየታያዩ ተወጡ።ቃለአብ ትምሀርት አቁሞ የእርዳታ ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ እየሰራ እንደሆነ ነገረው።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
"ዮርዲዬ ዛሬ ማዘሪቱን አስተዋውቅሀለሁ ተነስ እንሒድ"አለ
"አንተ ያምሀል እንዴ እኔ ትልቅ ሰው በጣም ነዉ እምፈራው።ደግሞ ምንድነው ብለህ ነው እምታስተዋውቀኝ"አለ ዮርዲ
"ዮርዲ ወንድሜ እኮ ነህ ።ምን ብየ እንዳስተዋውቅህ ነበር የፈለግከው?አሁን በል ተነስ"ብሎ ቃለ አብ ድርቅ አለ።
ዮርዲ እና ቃለአብ ግራና ቀኝ ሁነው ብስክሌቷን እየገፉ ወደ እነ ቃል ቤት አመሩ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ማርዘነብ ግሮሰሪ እንደደረሱ "ይቺ ናት ግሮሰሪያችን መተዳዳሪያችን።"አለ ቃል።
ከግሮሰሪው ጎን ባለው የግቢያቸው በር ወደ ዋናው ቤታቸው ዮርዲን ይዞት ገባ እና ቤት አስቀምጦት ወደ ግሮሰሪው ማርዘነብን ለመጥራት ገባ።
"እማዬ ዛሬ ወንድሜ ነው እያልኩሽ የነበረውን ጓደኛዬን አስተዋውቅሻለሁ።"ብሎ ወደቤት ማርዘነብን እየጎተተ ይዟት ገባ።
ማርዘነብ ዮርዲን እንዳየችው በድንጋጤ ክው ብላ ቀረች።መደንገጧ እንዳይታወቅባት "እእ......እ..አንተ ነህ የቃል ጓደኛ?"አለች የግዷን ፈገግ ብላ።

BY Ahadu picture


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/yegna_mastawesha/29

View MORE
Open in Telegram


Ahadu picture Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Tata Power whose core business is to generate, transmit and distribute electricity has made no money to investors in the last one decade. That is a big blunder considering it is one of the largest power generation companies in the country. One of the reasons is the company's huge debt levels which stood at ₹43,559 crore at the end of March 2021 compared to the company’s market capitalisation of ₹44,447 crore.

Start with a fresh view of investing strategy. The combination of risks and fads this quarter looks to be topping. That means the future is ready to move in.Likely, there will not be a wholesale shift. Company actions will aim to benefit from economic growth, inflationary pressures and a return of market-determined interest rates. In turn, all of that should drive the stock market and investment returns higher.

Ahadu picture from nl


Telegram Ahadu picture
FROM USA